Skip Navigation Links    
     





 

 
ከአበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሪ መጠን ለማሳደግ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው

Saturday, July 31, 2010

 
     
   

 

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23 2002 (ሬዲዮ ፋና) ሀገራችን ከአበባ ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ የምታገኘውን የውጭ ምንዛሪ መጠን በቀጣዮቹ አምስት አመታት ወደ አንድ ቢሊየን ዶላር ለማድረስ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑ ተጠቆመ።

 

          የኢትዮጵያ የአበባ አትክልትና ፍራፍሬ አምራችና ላኪዎች ማህበር ሊቀ መንበር አቶ ጸጋዬ አበበ ለሬዲዮ ፋና እንደተናገሩት ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከዘርፉ የምታገኘው አመታዊ ገቢ 216 ሚሊን ዶላር ብቻ ነው።

 

          ይህንን ገቢ በየአመቱ በ30 በመቶ በማሳደግ ሀገራችን ከአምስት አመታት በኋላ ከአበባ ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ የምታገኘውን የውጭ ምንዛሪ ወደ አንድ ቢሊየን ዶላር ለማድረስ የታቀደው።

 

          ጎረቤት ኬኒያ፤ ግብጽና ሞሮኮ በየአመቱ ከአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ብቻ ከግማሽ ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ እንደሚያገኙ ገልጸዋል።

 

ልማቱ ተግባራዊ ሲደረግም ከዘርፉ ወደ 1 ቢሊየን የሚጠጋ ገቢ እንደሚገኝና ለ200 ሺ ሰወች የስራ እድል እንደሚፈጠር ሊቀ መንበሩ ጠቁመዋል።

 

          ይህም የዘርፉን ገቢ ለማሳደግ ጠንካራ ስራ መስራት ይገባል ማለታቸውን ባልደረባችን አምሳለ ተስፋዬ ዘግባለች።

 
     
 
Other Stories

ወደ አገር ውስጥ የሚገባው ቀጥተኛ የውጭ ኢንቨስትመንት ፍሰት እያደገ ነው

በመረጃ ነጻነት ህግ ዙሪያ የተዘጋጀው የምክክር መድረክ ተጠናቀቀ

የተመዘገበው የኢኮኖሚ ዕድገት የተረጋጋ የኢኮኖሚ መሠረት መጣሉን የዓለም ገንዘብ ድርጅት አመለከተ

በአበባ እርሻ ልማት ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶች 250 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገቢ አገኙ

ከጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪው ዘርፍ አገሪቱን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው

በተመዘገበው የኢኮኖሚ ዕድገት የኅብረተሰቡ አኗኗር መቀየሩን በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ገለፁ

የምንዛሬ ተመን ማስተካከያው የተጀመረውን ዕድገት ለማስቀጠል ይረዳል ተባለ

የመረጃ ነጻነት ህግ አገራዊ ተፈጻሚነት እንዲኖረው ነጻ በሆነ መልኩ መፈጸም ይኖርበታል ተባለ

የውጭ ምንዛሪ ተመን ለውጡ የወጪ ንግድን ለማጠናከር ይረዳል --- የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት

አዲሱ የከፍተኛ ትምህርት መመሪያ ጥራትን ለማረጋገጥ የተቀረፀ መሆኑ ተጠቆመ