Skip Navigation Links    
     





 

 
ስምምነቱ የሕዝቦችን የጋራ ጥቅም ያገናዘበ መሆኑን የኦብነግ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ገለጹ

Saturday, July 31, 2010

 
     
   

አዲስአበባሐምሌ24 2002 (ሬዲዮፋና)በኢትዮጵያ መንግሥትና በተባበረው የምዕራብ ሶማሌ ነጻ አውጪ ግንባር መካከል የተፈረመው የሰላም ስምምነት የሕዝቦች የጋራ ጥቅም ያገናዘበ መሆኑንየኦጋዴን ብሔራዊ ነጻ አውጪ ግንባር (ኦብነግ) ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ገለጹ፡፡

የድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ አብዱላሂ አህመድ ኢብራሂም  ለኢዜአ እንደተናገሩት በሁለቱ ወገኖች የተደረሰው ስምምነት የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው፡፡

ይህም በክልሉ ብሎም በአገሪቱ የተጀመረው የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች አጠናክሮ ለመቀጠል መልካም አጋጣሚ የሚፈጥር ነው ብለዋል፡፡

የሶማሌ ክልል ሕዝብ በአገሪቱ ከተጀመረው ልማትና ዴሞክራሲ ተጠቃሚ መሆን መቻሉ እንደ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻ አውጪ ግንባር ያሉ ኃይሎች ወደ ሰላማዊ መንገድ እንዲመለሱ ጫና እያሳደረባቸው መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

ድርጅታቸው ሕዝቡ ባሳደረበትን ጫና ተከታታይ ውይይትና ግምገማ በማድረግ እንደ ቀሪው የአገሪቱ ሕዝብ የልማትና የዕድገት ጎዳናውን በመምረጥ ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ መወሰኑን አቶ አብዱላሂ ተናግረዋል፡፡

በዚህም ከግንባሩ ሦስት አራተኛው የሚበልጡ የአመራር አባላት በሕገ-መንግሥቱ ጥላ ሥር ሆነው ዓላማቸውን ለማስፈጸም መስማማታቸውን ገልጸዋል፡፡

ሲሶ የማይሞላው ከኦብነግ ያፈነገጠው አንጃ የሕዝብ ድጋፍ እንደሌለው አቶ አብዱላሂ አስታውቀዋል፡፡

ከኢትዮጵያ መንግሥትጋር እየተደረገ ያለው ስምምነት ልክ የተባበረውየምዕራብ ሶማሌ ነጻ አውጪግንባርእንዳደረገው ሁሉ፤ስኬታማ እንደሚሆንም እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡

ከግንባሩ ጋር የተደረሰው ስምምነት ሕዝቦች እጅ ለእጅ ተያይዘው በጋራ ልማትን ለማፋጠን የሚያስችል በመሆኑ አብነግም ለሰላም መቆሙን ማረጋገጥ ይገባዋል ብለዋል፡፡

አቶ አብዱላሂ አህመድ ኢብራሂም የግንባሩ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ከመሆናቸው ሌላ፤ በአሥመራ የኦብነግ ጽህፈት ቤት ኃላፊ በመሆን ለአምስት ዓመታት ማገልገላቸውን መናገራቸውን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል፡፡

 

 
     
 
Other Stories

ወደ አገር ውስጥ የሚገባው ቀጥተኛ የውጭ ኢንቨስትመንት ፍሰት እያደገ ነው

በመረጃ ነጻነት ህግ ዙሪያ የተዘጋጀው የምክክር መድረክ ተጠናቀቀ

የተመዘገበው የኢኮኖሚ ዕድገት የተረጋጋ የኢኮኖሚ መሠረት መጣሉን የዓለም ገንዘብ ድርጅት አመለከተ

በአበባ እርሻ ልማት ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶች 250 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገቢ አገኙ

ከጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪው ዘርፍ አገሪቱን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው

በተመዘገበው የኢኮኖሚ ዕድገት የኅብረተሰቡ አኗኗር መቀየሩን በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ገለፁ

የምንዛሬ ተመን ማስተካከያው የተጀመረውን ዕድገት ለማስቀጠል ይረዳል ተባለ

የመረጃ ነጻነት ህግ አገራዊ ተፈጻሚነት እንዲኖረው ነጻ በሆነ መልኩ መፈጸም ይኖርበታል ተባለ

የውጭ ምንዛሪ ተመን ለውጡ የወጪ ንግድን ለማጠናከር ይረዳል --- የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት

አዲሱ የከፍተኛ ትምህርት መመሪያ ጥራትን ለማረጋገጥ የተቀረፀ መሆኑ ተጠቆመ