አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22 2002 (ሬዲዮ ፋና) በቀጣዩ አመት ታህሳስ ወር በጋና አክራ ለሚካሄደው የአፍሪካ ኢንተርፕርነር ሺፕ ሽልማት ኢትዮጵያ ተመረጠች።
ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ኢንተርፕርነር ሺፕ ሽልማት የታጨችው ከ15 የአፍሪካ ሀገራት መካከል ተመርጣ መሆኑ ተጠቁሟል።
እንድ ሮይተርስ ዘገባ የሌጋተም አፍሪካ ሽልማት መርሀ ግብር የአፍሪካ የንግድ አመራሮችን በማበረታታት ለስራቸው እውቅና ሰጥቶ ሽልማት መስጠት ላይ ያተኩራል።
ለተሸላሚዎች 350ሺ የአሜሪካ ዶላር መዘጋጀቱንና ቀዳማይ ተሸላሚው አንድ መቶ ሺ ዶላር ያገኛል።